ስለ እኛ

About Our Parish

ታሪካችን እና እምነታችን History & Faith

የዊኒፔግ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በካናዳ ማኒቶባ ግዛት ለሚኖሩ ምእመናን መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት የተመሰረተች የተቀደሰች ማህበረሰብ ናት። ቤተ ክርስቲያናችን ጥንታዊቷንና ሐዋርያዊቷን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን፣ ሥርዓትንና ባህልን ጠብቃ ለትውልድ ታስተላልፋለች።

Debre Genet Holy Mary Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Winnipeg is a sacred community dedicated to serving the spiritual needs of the faithful in Manitoba. We uphold the ancient, apostolic faith, traditions, and liturgical practices of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, preserving them for future generations.

ተልእኳችን እና ራእያችን Mission & Vision
SPIRITUAL GROWTH የምእመናንን መንፈሳዊ ሕይወት በጸሎት፣ በቅዳሴና በትምህርተ ወንጌል ማነጽ።
CULTURAL HERITAGE የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክና ቋንቋ (ግዕዝን) ማስተማር።
COMMUNITY በዊኒፔግና አካባቢዋ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ለሁሉም ምእመናን መጠለያና አንድነት መሆን።
የማህበረሰብ አገልግሎት Our Community in Winnipeg

ቤተ ክርስቲያናችን ከመንፈሳዊ አገልግሎት በተጨማሪ ለወጣቶች የሰንበት ትምህርት ቤት፣ የቋንቋ ትምህርት (አማርኛና ግዕዝ)፣ እንዲሁም አዲስ ለሚመጡ ወገኖች ማህበራዊ ድጋፍ በመስጠት ላይ ትገኛለች። በዊኒፔግ የሚገኘውን አዲሱን የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ለመገንባት በምናደርገው ጥረት ላይ ሁሉም እንዲሳተፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

Beyond liturgical services, our parish provides Sunday School for youth, language classes (Amharic and Ge'ez), and social support for newcomers. We invite all to participate in our historic journey as we work toward building our permanent sanctuary in the heart of Winnipeg.